Fasiledes High School The new building
Education is the ultimate gateway to development

Education is the ultimate gateway to development
ምንም እንኳን እያዘገመም ቢሆን የፋሲለደስ ሁለተኛ ደረጃ ት/ቤት የአዲስ ህንፃ ግንባታው ሲካሄድ የነበረ ቢሆንም፣ አሁን ግን በቅን አሳቢና ተቆርቋሪዎች አማካኝነት በተደረገ ርብርብ፣ የህንፃው ግንባታ እየተገባደደ በቅርቡ ተጠናቆ ለአግልግሎት የሚደርስ መሆኑን ስንገልፅ በትልቅ እፎይታና ደስታ ነው፡፡
በአሜሪካ የሚገኘው የግንባታው አስተባባሪ ቡድን በተጨማሪ ያደረገው ቢኖር፣ ለዚህ አመት የሁለተኛ ደረጃ መልቀቂያ ፈተና የሚቀመጡ ተማሪዎችን ለፈተና እንዲዘጋጁ በማለት፣ ጎንደር በሚገኘው የህንፃው አሠሪ ኮሚቴ ጋር በመተባበር፣ የትምህርት ቤቱ መምህራን ለተማሪዎቹ የፈተና መዘጋጃ ትምህርት እንዲሠጡ በማድረግ በጀት መድቦ ፕሮጀክቱ እንዲጠና ቀ ቅ አድርጋጓል፡፡ ለዚህም ሲባል 1.2 ሚሊዮን ብር አገልግሎት ላይ ውሏል፡፡ ወጭው የተሸፈነው ከግንባታ አስተባበሪው ቡድን በተላከ ገንዘብ ነው፡፡
የህንፃው መጠናቀቅ ለሁላችንም ታላቅ ስኬት ቢሆንም፣ ትምህርት በጥራት እንዲሰጥ ለማድረግ፣ በተለይም ከዚሁ ት/ቤት የሁለተኛ ደረጃ መልቀቂያ ፈተናውን የሚያልፉ ተማሪዎችን ቁጥር ከፍ ለማድረግ ጥረት እንደሚያሰፈልግ ሁላችንም እንገነዘባለን፡፡ ሰለዚህ ሁሉም በበኩሉ ለዚህ አስፈላጊ ለሆነ ትምህረትን ለማዳበር በሚደረገው ጥረት ድርሻውን እንዲወጣ ስንጠይቅ በታላቅ አክብሮት ነው፡፡ የገንዘብ አስተዋፅኦ ለማድረግ ለሚፈልጉ ለዚሁ ለት/ቤቱ ማሰሪያ በተከፈተው የጎፈንድሚ አካውንት ርደታ ማድረግ የሚችሉ መሆኑን በትህትና እንገልፃለን፡፡
ከምስጋና ጋር
አሰተባባሪ ቡድን
የተለየ አዲስ ለመስራት ሳይሆን ለአመታት ብዙ ተማሪዎችን ያስመረቀው የፋሲለደስ ት/ቤት ህንፃ በማርጀቱ የትምህርት ገበታ ላይ ባሉ ተማሪዎችና መምህራን እላያቸው ላይ ይናዳል የሚል ሥጋት በመፈጠሩ፣ በተጨማሪም በዚህ ሥጋት ምክንያት አንዳንዶች ህንጻዎች ለአገልገሎት እንዳይውሉ መታገዳቸውን በመመልከት፣ ትውልድ አሻጋሪ የሆነው ትምህርት ተጓጉሎ ትውልድ ወደኋላ መቅረቱ ያሳሰባቸው ተቆርቋሪዎች ት/ቤቱን በአዲስ መልክ ለመሥራት፣ የከተማው ነዋሪ ዜጎች፣ የጎንደር ዩኒቨርሲቲ ባለሙያተኞች እናም ሌሎች ተቆርቋሪዎች፣ ከሀገር ውጭ ደግሞ በፋሲለደስ መረዳጃ ማህበር ስር የተደራጁ ዜጎች ተነጋግረው አስፈላጊው ጥናትና መዋቅር ከተዘጋጀ በኋላ፣ በውጭ አገር ግን የት/ቤቱን ሥራ በሚመለከት ከፋሲለደሰ መረዳጃ በላይ ሰፋ በማለት አዲስ አሰተባባሪ ቡድን በማዋቀር እንቅስቃሴ ተጀመረ፡፡
ማሳሰቢያ በጎፈንድሚ የሚለግሱ ከሆነ
So far with fewer individuals than expected the school project is underway. Understanding the several issues, however we think this is as important as any thing especially for the future generation. With affordable smaller but from so many we can achieve our goal.
For questions please contact Menen Tesfahun 408 228 224
Founding Core Executive Committee
Founding Core Executive Committee
Past members
Past Advisory members
Stake holders:-
We use cookies to analyze website traffic and optimize your website experience. By accepting our use of cookies, your data will be aggregated with all other user data.