The New Fasiledes High School Building
ከህንፃ ግንባታ ወደ ትውልድ ግንባታ

ከህንፃ ግንባታ ወደ ትውልድ ግንባታ


With the completion of the school building, the Fasiledes school construction organizing group would like to extend a token of gratitude. However, for most of you we could not get your contact information. Therefore, if you desire to get the certificate seen here, please contact the organizing using the send a request button. Please include your email to recive the signed certificate. please write your name as you want it to be on the certificate.
Unfortunately, we could not have your names written or itched on a wall due to several reasons and we apologize.
Thank you


The new Fasiledes High school builidng soon to start.
Students who got additional tuition for the school leaving exam passed at an unbelievable rate. (75 - 90% pass)

Our group is made up of committed volunteer individuals.
Founding Core Executive Committee
Advisory members

የፋሲለደስ ግንባታ አስተባባሪ ቡድን፣ ከህንፃው ግንባታ በተጨማሪ፣ በትምህርቱም ላይ በማተኮር፣
ለህንፃ ማሠሪያው ከተሰበሰበው ጎፈንድሚ ከተረፈች ትንሽ ገንዘብና በተጨማሪም የአስተባባሪው ቡድን አባላት በየግላቸው ተጨማሪ አስተዋፅኦ በማድረግ፣ የፋሲለደስ ቁጥር 1ና 2 ተማሪዎች ለ2017 መልቀቂያ ፈተና እንዲዘጋጁ በጀት በመመደብ፣ በት/ቤቱ አሠሪ ኮሜቴ፣ በርዕሰ መመህሩና በመምህራኑ በኩል የማጠናከሪያ ትምህርት እንዲሠጣቸው ተደርጎ የተገኘው ውጤት ሁሉንም ዜጋ የሚያስደስት መሆኑን ለመጋራት እንወዳለን፡፡
በመረጃ በርዕሰ መምህሩ በእንዳለ ታደሰ ወልደስላሴ በተላከልን የተማሪዎችን ውጤት ለማሳወቅ በሚል ደብዳቤ
ውጤቱ እንደሚከተለው ነው
በፋሲለደስ ግንባታ ቁጥር 1 ትምህረት ቤት ለ300 ተማሪዎች የማጠናከሪያ ትምህርት የተሠጠ ሲሆን፣ ከነዚህ መሀከል 270 ተማሪዎች የዩኒቨርሲቲ መግቢያ ውጤት አስመዝገበዋል፡፡ በፐርስንት ሲታይ ዘጠና ፐርሰንት (90%)
በተጨማሪም ከነዚህ መሀከል 15 ተማሪዎች ከ 495 – 534 ከፍተኛ ነጥብ አግኝተዋል፡፡
ሁላችንም እንኳን ደስ ያለን
የፋሲለደስ ቁ 2 የተወሰኑ ተማሪዎችም የማጠናከሪያ ትምህርት የተሠጣቸው ሲሆን ዝርዝሩ ለጊዜው ባይደርሰንም
ባጠቃላይ በቁጥር 1ና2 500 ተማሪዎች የማጠናከሪያ ትምህርት ተሠጥቷቸዋል፡፡ ከቁ 2 ጋር ሲደመር ለዩኒቨርሲቴ ያለፉት ተማሪዎች 377 ነው፡፡ ይህም በፐርሰንት ሲታይ 75.5% ነው፡፡
እንደገናም አንኳን ደስ ያለን፡
የተለየ አዲስ ለመስራት ሳይሆን ለአመታት ብዙ ተማሪዎችን ያስመረቀው የፋሲለደስ ት/ቤት ህንፃ በማርጀቱ የትምህርት ገበታ ላይ ባሉ ተማሪዎችና መምህራን እላያቸው ላይ ይናዳል የሚል ሥጋት በመፈጠሩ፣ በተጨማሪም በዚህ ሥጋት ምክንያት አንዳንዶች ህንጻዎች ለአገልገሎት እንዳይውሉ መታገዳቸውን በመመልከት፣ ትውልድ አሻጋሪ የሆነው ትምህርት ተጓጉሎ ትውልድ ወደኋላ መቅረቱ ያሳሰባቸው ተቆርቋሪዎች ት/ቤቱን በአዲስ መልክ ለመሥራት፣ የከተማው ነዋሪ ዜጎች፣ የጎንደር ዩኒቨርሲቲ ባለሙያተኞች እናም ሌሎች ተቆርቋሪዎች፣ ከሀገር ውጭ ደግሞ በፋሲለደስ መረዳጃ ማህበር ስር የተደራጁ ዜጎች ተነጋግረው አስፈላጊው ጥናትና መዋቅር ከተዘጋጀ በኋላ፣ በውጭ አገር ግን የት/ቤቱን ሥራ በሚመለከት ከፋሲለደሰ መረዳጃ በላይ ሰፋ በማለት አዲስ አሰተባባሪ ቡድን በማዋቀር እንቅስቃሴ ተጀመረ፡፡
We use cookies to analyze website traffic and optimize your website experience. By accepting our use of cookies, your data will be aggregated with all other user data.