ከህንፃ ግንባታ ወደ ትውልድ ግንባታ

ከህንፃ ግንባታ ወደ ትውልድ ግንባታ


SUCCESFUL MISSION
To all supporters of this project
After a long arduous process, finally, the school construction is completed. Official inauguration was made in January of 2026. This could happen with collaboration of individuals, organizations and relentless work of the school construction committee in Gondar. Additionally, this organizing group was able to accomplish its task using the structure of the Non-profit organization, Fasiledes Meredaja Maheber.
Thanking all, we officially announce that this project is over and the organizing group will cease as a group and with no further relationship with Fasiledes Meredaja Mahber. And the GoFundMe account opened for this purpose will be deactivated or will not be used further.
As education is a gateway to development and life changing event for individuals, we are still financing the second round of special tuition for students who are going to sit for 2018 E.C year school leaving exam. We hope to see the result we saw in 1917, a 90% passing rate.
Fasiledes School Construction Organizing Group


The new Fasiledes High school builidng soon to start.
Amazing success: Students who got additional tuition for the school leaving exam passed at an unbelievable rate. (75 - 90% pass)

Our group is made up of committed volunteer individuals.
Founding Core Executive Committee
Advisory members

የፋሲለደስ ግንባታ አስተባባሪ ቡድን፣ ከህንፃው ግንባታ በተጨማሪ፣ በትምህርቱም ላይ በማተኮር፣
ለህንፃ ማሠሪያው ከተሰበሰበው ጎፈንድሚ ከተረፈች ትንሽ ገንዘብና በተጨማሪም የአስተባባሪው ቡድን አባላት በየግላቸው ተጨማሪ አስተዋፅኦ በማድረግ፣ የፋሲለደስ ቁጥር 1ና 2 ተማሪዎች ለ2017 መልቀቂያ ፈተና እንዲዘጋጁ በጀት በመመደብ፣ በት/ቤቱ አሠሪ ኮሜቴ፣ በርዕሰ መመህሩና በመምህራኑ በኩል የማጠናከሪያ ትምህርት እንዲሠጣቸው ተደርጎ የተገኘው ውጤት ሁሉንም ዜጋ የሚያስደስት መሆኑን ለመጋራት እንወዳለን፡፡
በመረጃ በርዕሰ መምህሩ በእንዳለ ታደሰ ወልደስላሴ በተላከልን የተማሪዎችን ውጤት ለማሳወቅ በሚል ደብዳቤ
ውጤቱ እንደሚከተለው ነው
በፋሲለደስ ግንባታ ቁጥር 1 ትምህረት ቤት ለ300 ተማሪዎች የማጠናከሪያ ትምህርት የተሠጠ ሲሆን፣ ከነዚህ መሀከል 270 ተማሪዎች የዩኒቨርሲቲ መግቢያ ውጤት አስመዝገበዋል፡፡ በፐርስንት ሲታይ ዘጠና ፐርሰንት (90%)
በተጨማሪም ከነዚህ መሀከል 15 ተማሪዎች ከ 495 – 534 ከፍተኛ ነጥብ አግኝተዋል፡፡
ሁላችንም እንኳን ደስ ያለን
የፋሲለደስ ቁ 2 የተወሰኑ ተማሪዎችም የማጠናከሪያ ትምህርት የተሠጣቸው ሲሆን ዝርዝሩ ለጊዜው ባይደርሰንም
ባጠቃላይ በቁጥር 1ና2 500 ተማሪዎች የማጠናከሪያ ትምህርት ተሠጥቷቸዋል፡፡ ከቁ 2 ጋር ሲደመር ለዩኒቨርሲቴ ያለፉት ተማሪዎች 377 ነው፡፡ ይህም በፐርሰንት ሲታይ 75.5% ነው፡፡
እንደገናም አንኳን ደስ ያለን፡
የተለየ አዲስ ለመስራት ሳይሆን ለአመታት ብዙ ተማሪዎችን ያስመረቀው የፋሲለደስ ት/ቤት ህንፃ በማርጀቱ የትምህርት ገበታ ላይ ባሉ ተማሪዎችና መምህራን እላያቸው ላይ ይናዳል የሚል ሥጋት በመፈጠሩ፣ በተጨማሪም በዚህ ሥጋት ምክንያት አንዳንዶች ህንጻዎች ለአገልገሎት እንዳይውሉ መታገዳቸውን በመመልከት፣ ትውልድ አሻጋሪ የሆነው ትምህርት ተጓጉሎ ትውልድ ወደኋላ መቅረቱ ያሳሰባቸው ተቆርቋሪዎች ት/ቤቱን በአዲስ መልክ ለመሥራት፣ የከተማው ነዋሪ ዜጎች፣ የጎንደር ዩኒቨርሲቲ ባለሙያተኞች እናም ሌሎች ተቆርቋሪዎች፣ ከሀገር ውጭ ደግሞ በፋሲለደስ መረዳጃ ማህበር ስር የተደራጁ ዜጎች ተነጋግረው አስፈላጊው ጥናትና መዋቅር ከተዘጋጀ በኋላ፣ በውጭ አገር ግን የት/ቤቱን ሥራ በሚመለከት ከፋሲለደሰ መረዳጃ በላይ ሰፋ በማለት አዲስ አሰተባባሪ ቡድን በማዋቀር እንቅስቃሴ ተጀመረ፡፡
We use cookies to analyze website traffic and optimize your website experience. By accepting our use of cookies, your data will be aggregated with all other user data.